96|1|አንብብ በዚያ (ሁሉን) በፈጠረው ጌታህ ስም፡፡
96|2|ሰውን ከረጋ ደም በፈጠረው (ጌታህ ስም)፡፡
96|3|አንብብ፤ ጌታህ በጣም ቸር ሲኾን፤
96|4|ያ በብርዕ ያስተማረ፡፡
96|5|ሰውን ያላወቀውን ሁሉ ያሳወቀ ሲኾን፡፡
96|6|በእውነቱ ሰው ወሰንን ያልፋል፡፡
96|7|ራሱን የተብቃቃ (ባለ ሀብት) ኾኖ ለማየቱ፡፡
96|8|መመለሻው ወደ ጌታህ ብቻ ነው፡፡
96|9|አየህን? ያንን የሚከለክለውን፡፡
96|10|ባሪያን በሰገደ ጊዜ፤
96|11|አየህን? ንገረኝ (ተከልካዩ) በትክክለኛ መንገድ ላይ ቢኾን፤
96|12|ወይም (ፈጣሪውን) በመፍራት ቢያዝ፤
96|13|አየህን? ንገረኝ (ከልካዩ) ቢያስተባብልና (ከእምነት) ቢሸሽ፤
96|14|አላህ የሚያይ መኾኑን አያውቅምን?
96|15|ይተው ባይከለከል አናቱን ይዘን እንጎትተዋለን፡፡
96|16|ውሸታም ስሕተተኛ የኾነችውን አናቱን፡፡
96|17|ሸንጎውንም ይጥራ፡፡
96|18|(እኛም) ዘበኞቻችንን እንጠራለን፡፡
96|19|ይከልከል አትታዘዘው፡፡ ስገድም፤ (ወደ አላህ) ተቃረብም፡፡
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114