86|1|በሰማዩ በሌሊት መጪውም እምላለሁ፡፡
86|2|የሌሊት መጪውም ምን እንደ ኾነ ምን አሳወቀህ?
86|3|ጨለማን ቀዳጁ ኮከብ ነው፡፡
86|4|ነፍስ ሁሉ በእርሷ ላይ ጠባቂ ያለባት እንጅ ሌላ አይደለችም፡፡
86|5|ሰውም ከምን እንደተፈጠረ ይመልከት፡፡
86|6|ከተስፈንጣሪ ውሃ ተፈጠረ፡፡
86|7|ከጀርባና ከእርግብግብቶች መካከል የሚወጣ ከኾነ (ውሃ)፡፡
86|8|እርሱ (አላህ) በመመለሱ ላይ በእርግጥ ቻይ ነው፡፡
86|9|ምስጢሮች በሚገለጡበት ቀን፡፡
86|10|ለእርሱም (ለሰው) ኀይልና ረዳት ምንም የለውም፡፡
86|11|የመመለስ ባለቤት በኾነችው ሰማይም እምላለሁ፡፡
86|12|(በበቃይ) የመሰንጠቅ ባለቤት በኾነችው ምድርም፤
86|13|እርሱ (እውነትን ከውሸት) የሚለይ ቃል ነው፡፡
86|14|እርሱም ቀልድ አይደለም፡፡
86|15|እነርሱ በእርግጥ ተንኮልን ይሠራሉ፡፡
86|16|(እኔ) ተንኮልንም እመልሳለሁ፡፡
86|17|ከሓዲዎችንም ቀን ስጣቸው፡፡ ጥቂትን ጊዜ አቆያቸው፡፡
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114