82|1|ሰማይ በተሰነጠቀች ጊዜ፤
82|2|ከዋክብትም ተበታትነው በወደቁ ጊዜ፤
82|3|ባሕሮችም በተከፈቱና በተደበላለቁ ጊዜ፤
82|4|መቃብሮችም በተገለባበጡና (ሙታን) በተነሱ ጊዜ፤
82|5|ማንኛይቱም ነፍስ ያስቀደመችውንና ያቆየችውን ታውቃለች፡፡
82|6|አንተ ሰው ሆይ! በቸሩ ጌታህ ምን አታለለህ?
82|7|በዚያ በፈጠረህ አካለ ሙሉም ባደረገህ ባስተካከለህም፡፡
82|8|በማንኛውም በሻው ቅርፅ በገጣጠመህ (ጌታህ ምን አታለለህ)፡፡
82|9|ተከልከሉ፤ በእውነቱ በፍርዱ ቀን ታስተባብላላችሁ፡፡
82|10|በእናንተ ላይ ተጠባባቂዎች ያሉባችሁ፤ ስትኾኑ፤
82|11|የተከበሩ ጸሐፊዎች የኾኑ፤ (ተጠባባቂዎች)፡፡
82|12|የምትሠሩትን ሁሉ የሚያውቁ፡፡
82|13|እውነተኞቹ ምእምናን በእርግጥ በገነት ውስጥ ናቸው፡፡
82|14|ከሓዲዎቹም በእርግጥ በገሀነም ውስጥ ናቸው፡፡
82|15|በፍርዱ ቀን ይገቧታል፡፡
82|16|እነርሱም ከርሷ ራቂዎች አይደሉም፡፡
82|17|የፍርድ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
82|18|ከዚያም የፍርዱ ቀን ምን እንደኾነ ምን አሳወቀህ?
82|19|(እርሱ) ማንኛይቱም ነፍስ ለሌላይቱ ነፍስ ምንም ማድረግን የማትችልበት ቀን ነው፡፡ ነገሩም ሁሉ በዚያ ቀን ለአላህ ብቻ ነው፡፡
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114