88|1|የሸፋኝቱ (ትንሣኤ) ወሬ መጣህን?
88|2|ፊቶች በዚያ ቀን ተዋራጆች ናቸው፡፡
88|3|ሠሪዎች ለፊዎች ናቸው፡፡
88|4|ተኳሳን እሳት ይገባሉ፡፡
88|5|በጣም ከፈላች ምንጭ ይጋታሉ፡፡
88|6|ለእነርሱ ዶሪዕ ከሚባል (እሾሃም) ዛፍ እንጅ ሌላ ምግብ የላቸውም፡፡
88|7|የማያሰባ ከረኃብም የማያብቃቃ ከኾነው፡፡
88|8|ፊቶች በዚያ ቀን ተቀማጣዮች ናቸው፡፡
88|9|ለሥራቸው ተደሳቾች ናቸው፡፡
88|10|በከፍተኛ ገነት ውስጥ ናቸው፡፡
88|11|በውስጧ ውድቅን ነገር አይሰሙም፡፡
88|12|በውስጧ ፈሳሾች ምንጮች አልሉ፡፡
88|13|በውስጧ ከፍ የተደረጉ አልጋዎች አልሉ፡፡
88|14|በተርታ የተኖሩ ብርጭቆዎችም፡፡
88|15|የተደረደሩ መከዳዎችም፡፡
88|16|የተነጠፉ ስጋጃዎችም (አልሉ)፡፡
88|17|(ከሓዲዎች) አይመለከቱምን? ወደ ግመል እንዴት እነደተፈጠረች!
88|18|ወደ ሰማይም እንዴት ከፍ እንደ ተደረገች!
88|19|ወደ ተራራዎችም እንዴት እንደ ተቸከሉ!
88|20|ወደ ምድርም እንዴ እንደተዘረጋች (አይመለከቱምን?)
88|21|አስታውስም፤ አንተ አስታዋሽ ብቻ ነህና፡፡
88|22|በእነርሱ ላይ ተሿሚ (አስገዳጅ) አይደለህም፡፡
88|23|ግን (ከእውነት) የዞረና የካደ ሰው፤
88|24|አላህ ታላቁን ቅጣት ይቀጣዋል፡፡
88|25|መመለሻቸው ወደእኛ ብቻ ነው፡፡
88|26|ከዚያም ምርመራቸው በእኛ ላይ ብቻ ነው፡፡
Amharic Quran
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114