91|1|በፀሐይና በብርሃኗ እምላለሁ፡፡
91|2|በጨረቃም በተከተላት ጊዜ፤
91|3|በቀኑም (ፀሐይን) በገለጻት ጊዜ፤
91|4|በሌሊቱም በሸፈናት ጊዜ፤
91|5|በሰማይቱም በገነባትም (ጌታ)፤
91|6|በምድሪቱም በዘረጋትም፤
91|7|በነፍስም ባስተካከላትም፤
91|8|አመጽዋንና ፍርሃትዋንም ባሳወቃት (አምላክ እምላለሁ)፡፡
91|9|(ከኀጢኣት) ያጠራት ሰው ፍላጎቱን በእርግጥ አገኘ፡፡
91|10|(በኀጢኣት) የሸፈናትም ሰው በእውነት አፈረ፡፡
91|11|ሠሙድ ወሰን በማለፍዋ አስተባበለች፡፡
91|12|ጠማማዋ በተንቀሳቀሰ ጊዜ፡፡
91|13|ለእነርሱም የአላህ መልክተኛ (ሷሊህ) «የአላህን ግመል የመጠጥ ተራዋንም (ተጠንቀቁ)» አላቸው፡፡
91|14|አስተባበሉትም፡፡ (ቋንጃዋን) ወጓትም፡፡ በኀጢኣታቸውም ምክንያት ጌታቸው (ቅጣትን) በእነርሱ ላይ ደመደመባቸው፤ አስተካከላትም፡፡
91|15|ፍጻሜዋንም (የምታስከትለውን) አያፈራም፡፡
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114