90|1|በዚህ አገር (በመካ) እምላለሁ፡፡
90|2|አንተ በዚህ አገር ሰፋሪ ስትኾን፡፡
90|3|በወላጂም በወለዳቸውም ሰዎች (በአዳምና በዘሮቹ ሁሉ እምላለሁ)፡፡
90|4|ሰውን ሁሉ በእርግጥ በልፋት ውስጥ ኾኖ ፈጠርነው፡፡
90|5|በእርሱ ላይ አንድም የማይችል መኾኑን ይጠረጥራልን?
90|6|«ብዙን ገንዘብ አጠፋሁ» ይላል፡፡
90|7|አንድም ያላየው መኾኑን ያስባልን?
90|8|ለእርሱ ሁለት ዓይኖችን አላደረግንለትምን?
90|9|ምላስንና ሁለት ከንፈሮችንም፡፡
90|10|ሁለትን መንገዶችም አልመራነውምን?
90|11|ዓቀበቲቱንም አልወጣም፡፡
90|12|ዓቀበቲቱም (መውጣቷ) ምን እንደኾነች ምን አሳወቀህ?
90|13|(እርሱ) ጫንቃን መልቀቅ ነው፡፡
90|14|ወይም የረኃብ ባለቤት በኾነ ቀን ማብላት፡፡
90|15|የዝምድና ባለቤት የኾነን የቲም፤
90|16|ወይም የዐፈር ባለቤት የኾነን ድኻ (ማብላት ነው)፡፡
90|17|(ዐቀበቲቱን አልወጣም)፡፡ ከዚያም ከነዚያ ከአመኑትና በመታገስ አደራ ከተባባሉት፣ በማዘንም አደራ ከተባባሉት ሰዎች አልኾነም፡፡
90|18|እነዚያ (ይህንን የፈጸሙ) የቀኝ ጓዶች ናቸው፡፡
90|19|እነዚያም በአንቀጾቻችን የካዱት እነርሱ የግራ ጓዶች ናቸው፡፡
90|20|በእነርሱ ላይ የተዘጋች እሳት አልለች፡፡
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114