92|1|በሌሊቱ እምላለሁ (በጨለማው) በሚሸፍን ጊዜ፡፡
92|2|በቀኑም፤ በተገለጸ ጊዜ፡፡
92|3|ወንድንና ሴትን በፈጠረውም (አምላክ እምላለሁ)፡፡
92|4|ሥራችሁ በእርግጥ የተለያየ ነው፡፡
92|5|የሰጠ ሰውማ ጌታውን የፈራም፡፡
92|6|በመልካሚቱም (እምነት) ያረጋገጠ፤
92|7|ለገሪቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
92|8|የሰሰተ ሰውማ የተብቃቃም፤ (በራሱ የተመካ)፤
92|9|በመልካሚቱ (እምነት) ያሰተባበለም፤
92|10|ለክፉይቱ ሥራ እናዘጋጀዋለን፡፡
92|11|በወደቀም ጊዜ ገንዘቡ ከእርሱ ምንም አይጠቅመውም፡፡
92|12|ቅኑን መንገድ መግለጽ በእኛ ላይ አለብን፡፡
92|13|መጨረሻይቱም መጀመሪያይቱም ዓለም የእኛ ናቸው፡፡
92|14|የምትንቀለቀልንም እሳት አስጠነቀቅኳችሁ (በላቸው)፡፡
92|15|ከጠማማ በቀር ሌላ የማይገባት የኾነችን፡፡
92|16|ያ ያስተባበለና ከትዕዛዝ የሸሸው፡፡
92|17|አላህን በጣም ፈሪውም በእርግጥ ይርቃታል፡፡
92|18|ያ የሚጥራራ ኾኖ ገንዘቡን (ለድኾች) የሚሰጠው፡፡
92|19|ለአንድም ሰው እርሱ ዘንድ የምትመለስ ውለታ የለችም፡፡
92|20|ግን የታላቅ ጌታውን ውዴታ ለመፈለግ (ይህንን ሠራ)፡፡
92|21|ወደፊትም በእርግጥ ይደሰታል፡፡
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114