81|1|ፀሐይ በተጠቀለለች ጊዜ፤
81|2|ከዋክብትም በረገፉ ጊዜ፤
81|3|ተራራዎችም በተነዱ ጊዜ፤
81|4|የዐሥር ወር እርጉዞች ግመሎችም (ያለጠባቂ) በተተዉ ጊዜ፤
81|5|እንስሳትም ሁሉ በተሰበሰቡ ጊዜ፤
81|6|ባሕሮችም በተቃጠሉ ጊዜ፤
81|7|ነፍሶችም (በየአካሎቻቸው) በተቆራኙ ጊዜ፤
81|8|በሕይወቷ የተቀበረችውም ሴት ልጅ በተጠየቀች ጊዜ፤
81|9|በምን ወንጀል እንደ ተገደለች፤
81|10|ጽሑፎችም በተዘረጉ ጊዜ፤
81|11|ሰማይም በተገሸለጠች ጊዜ፤
81|12|ገሀነምም በተነደደች ጊዜ፤
81|13|ገነትም በተቀረበች ጊዜ፤
81|14|ነፍስ ሁሉ (ከሥራ) ያቀረበችውን ታውቃለች፤
81|15|ተመላሾችም በኾኑት (ዐዋድያት) እምላለሁ፡፡
81|16|ኺያጆች ገቢዎች በኾኑት (ከዋክብት)፡፡
81|17|በሌሊቱም (ጨለማውን) በጠነሰሰ ጊዜ፤
81|18|በንጋቱም (በብርሃን) በተነፈሰ ጊዜ፤ (እምላለሁ)፡፡
81|19|እርሱ (ቁርኣን) የክቡር መልክተኛ ቃል ነው፡፡
81|20|የኀይል ባለቤት በዙፋኑ ባለ ቤት ዘንድ ባለሟል የኾነ፡፡
81|21|በዚያ ስፍራ ትእዛዙ ተሰሚ፤ ታማኝ የኾነ (መልክተኛ ቃል) ነው፡፡
81|22|ነቢያችሁም በፍጹም ዕብድ አይደለም፡፡
81|23|በግልጹ አድማስም በእርግጥ አይቶታል፡፡
81|24|እርሱም በሩቁ ወሬ ላይ ሰሳች (ንፉግ) አይደለም፡፡
81|25|እርሱም (ቁርኣን) የእርጉም ሰይጣን ቃል አይደለም፡፡
81|26|ታዲያ ወዴት ትኼዳላችሁ?
81|27|እርሱ የዓለማት መገሠጫ እንጅ ሌላ አይደለም፡፡
81|28|ከናንተ ቀጥተኛ መኾንን ለሻ ሰው (መገሰጫ ነው)፡፡
81|29|የዓለማት ጌታ አላህ ካልሻም አትሹም፡፡
Amharic Quran
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114