100|1|እያለከለኩ ሩዋጮች በኾኑት (ፈረሶች) እምላለሁ፡፡
100|2|(በሰኮናቸው) እያጋጩ እሳትን አውጪዎች በኾኑትም፤
100|3|በማለዳ ወራሪዎች በኾኑትም፤
100|4|በእርሱ አቧራን በቀሰቀሱትም፤
100|5|በ(ጠላት) ክቢ መካከል በእርሱ (በጧት) በተጋፈጡትም እምላለሁ፡፡
100|6|ሰው ለጌታው ብርቱ ከሓዲ ነው፡፡
100|7|እርሱም በዚህ ላይ መስካሪ ነው፡፡
100|8|እርሱም ገንዘብን ለመውደድ በጣም ብርቱ ነው፡፡
100|9|(ሰው) አያውቅምን? በመቃብሮች ያሉት (ሙታን) በተቀሰቀሱ ጊዜ፤
100|10|በልቦች ውስጥ ያለውም ሁሉ በተገለጸ ጊዜ (እንዴት እንደሚኾን)፡፡
100|11|ጌታቸው በዚያ ቀን በእነርሱ (ነገር) በእርግጥ ውስጠ አዋቂ ነው፡፡
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114