85|1|የቡርጆች ባለቤት በኾነችው ሰማይ እምላለሁ፡፡
85|2|በተቀጠረው ቀንም፤
85|3|በተጣጅና በሚጣዱትም፤ (እምላለሁ)፡፡
85|4|የጉድቡ ባለቤቶች ተረገሙ፡፡
85|5|የማገዶ ባለቤት የኾነቺው እሳት (ባለቤቶች)፡፡
85|6|እነርሱ በርሷ (አፋፍ) ላይ ተቀማጮች በኾኑ ጊዜ፤ (ተረገሙ)፡፡
85|7|እነርሱም በምእምናኖቹ በሚሠሩት (ማሰቃየት) ላይ መስካሪዎች ናቸው፡፡
85|8|ከእነርሱም በአላህ አሸናፊው፣ ምስጉኑ በኾነው (ጌታ) ማመናቸውን እንጅ ሌላ ምንም አልጠሉም፡፡
85|9|በእዚያ የሰማያትና የምድር ንግሥና ለእርሱ ብቻ በኾነው (አላህ ማመናቸውን)፡፡ አላህም በነገሩ ሁሉ ላይ መስካሪ ነው፡፡
85|10|እነዚያ ምእምንንና ምእምናትን ያሰቃዩ፣ ከዚያም ያልተጸጸቱ ለእነርሱ የገሀነም ቅጣት አልላቸው፡፡ ለእነርሱም የመቃጠሉ ስቃይ አልላቸው፡፡
85|11|እነዚያ ያመኑና መልካም ሥራዎችንም የሠሩ ለእነርሱ ከሥሮቻቸው ወንዞች የሚፈሱባቸው ገነቶች አሏቸው፡፡ ይህ ታላቅ ማግኘት ነው፡፡
85|12|የጌታህ በኀይል መያዝ ብርቱ ነው፡፡
85|13|እነሆ እርሱ መፍጠርን ይጀምራል፤ ይመልሳልም፡፡
85|14|እርሱም ምሕረተ ብዙ ወዳድ ነው፡፡
85|15|የዙፋኑ ባለቤት የላቀው ነው፡፡
85|16|የሚሻውን ሁሉ ሠሪ ነው፡፡
85|17|የሰራዊቶቹ ወሬ መጣልህን?
85|18|የፈርዖንና የሰሙድ፤ (ወሬ)፡፡
85|19|በእውነቱ እነዚያ የካዱት በማስተባበል ውስጥ ናቸው፡፡
85|20|አላህም በዙሪያቸው (በዕውቀቱ) ከባቢ ነው፡፡
85|21|ይልቁንም እርሱ የከበረ ቁርኣን ነው፡፡
85|22|የተጠበቀ በኾነ ሰሌዳ ውስጥ ነው፡፡
Amharic Quran
Pages: 1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21 22 23 24 25 26 27 28 29 30 31 32 33 34 35 36 37 38 39 40 41 42 43 44 45 46 47 48 49 50 51 52 53 54 55 56 57 58 59 60 61 62 63 64 65 66 67 68 69 70 71 72 73 74 75 76 77 78 79 80 81 82 83 84 85 86 87 88 89 90 91 92 93 94 95 96 97 98 99 100 101 102 103 104 105 106 107 108 109 110 111 112 113 114